የእምነት አቋም

1- መጽሐፍ ቅዱስ (66 መጽሐፍት) ትክክለኛ እና እውነተኛ እንዲሁም የማይለወጥ የእግዚአብሔር አስትንፋሳዊ ቃል እንደሆነ እናምናለን፡፡ ስለሆነም ብቸኛ የእምነት እና የሕይወት የመጨረሻ ሥልጣን አለው። ምሳሌ 30:5-6 ኢሳይያስ 8:20 ዮሐንስ 10:35 2 ጢሞቴዎስ 3:16-17 2 ጴጥሮስ 1:21

2-  እግዚአብሔር በአንድነትና በሶስትነት ለዘላለም ጸንቶ የሚኖር አምላክ እንደሆነ፤ በመለኮት አንድ ሲሆን በአካል ሶስት እንደሆነ እናምናለን (አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ)፡፡ ዘዳግም 6:4፣ ማቴዎስ 28:19፣ ዮሃንስ 14:26፣ 2 ቈረንቶስ 13:14፡፡

3እግዚአብሔር አብ አባት ሲሆን ሁሉን የሚችልና ሁሉን የሚገዛ ዘላለማዊ አምላክ እንደ ሆነ እናምናለን፡፡

4እግዚአብሔር አጽናፈ አለምን ከምንም እንደፈጠረና ፍጥረትም ሁሉ ከመጀመሪያ  መልካም እንደ ነበረ እናምናለን። ዘፍጥረት 1-2፣ ዘጸአት 20:11፣ እብራውያን 11:3

5እግዚአብሄር ሰውን በአምሳሉና በመልኩ እንደ ፈጠረ እንዲሁም የፍጥረት ሁሉ ገዥ እንዳደረገው እናምናለን። ዘፍጥረት 1:26-28፣ መዝሙር 8፣ ኢሳይያስ 43:7 ራእይ 4:11 መዝሙር 37:4

6ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተስፋው ቃል የእስራኤል መሲሕ እንደሆነና ፍፁም አምላክ፣ ፍፁም ሰው እንደሆነ እናምናለን። ማቴዎስ 1:21-23 ዮሃንስ 1:1, 14 20:28 እብራውያን 1:1-4 2:14

7ኢየሱስ ከድንግል እንደተወለደና ለአብ ፈጽሞ እንደታዘዘ እናምናለን፤ እንዲሁም ድንቅና ተአምራትን እንዳደረገ፣ በመስቀል ላይ እንደ ሞተ፣ በሶስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ እንደ ተነሳና ወደ ሰማይ አርጎ በሁሉ ላይ እንደ ነገሰ እናምናለን። ሉቃስ 1:26-35 እብራውያን 4:15 ዮሃንስ 14:11 ሉቃስ 23-24 ኤፌሶን 1:20-23

8መንፈስ ቅዱስ ልክ እንደ አብ እና ወልድ የመለኮት ባሕርያት ሁሉ ያሉት ፍጹም አምላክ እንደሆነና አምልኮ እንዲሁም ስግደት እንድሚገባው እናምናለን፡፡

9ሰው በኃጢአት እንደ ወደቀና እራሱን ማዳን እንደማይችል እናምናለን። ዘፍጥረት 3፣ ሮሜ 3:12, 23፣ ሮሜ 5:12

10- መዳን ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ስጦታ ስለሆነ በክርስቶስ በማመን ምንቀበለው እንጅ በስራ እንደማናገኘው እናምናለን ዮሃንስ 3:16 ሮሜ 1:16-17 ገላትያ 2:16-21

11- መንፈስ ቅዱስ አዲስ ልደት እንደሰጠንና ከክርስቶስ ጋር አንድ አካል እንዳደረገን፣ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ፍቅር እንደሚያረጋግጥልን፣ ወደ እውነት እንደሚመራን፣ በጸጋ ስጦታዎቹ እንደሚያስታጥቀንና ኃይል እንደሚሰጠን እናምናለንል። ዮሃንስ 3:3-8 ግብሪ ሃዋርያት 1:8 ሮሜ 8 1 ቈረንቶስ 12 ገላትያ 5:16-26 ኤፌሶን 3:16-21

12-  ቤተ ክርስቲያን በዘመናት መካከል ከሕዛብ ሁሉ በክርስቶስ የተጠሩ ሰዎች ህብረትና የክርስቶስ አካል እንደሆነች እናምናልን። ሮሜ 12:5፣ ገላትያ 3:26-29፣ ኤፌሶን 1:22-23፣ ራእይ 7:9

13- ዳግም የተወለደ አማኝ ሁሉ በአብ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም በውኃ በመጠመቅ ከክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ጋር መተባበሩን እንዲሁም ለኃጢአት ሞቶ ለጽድቅ መነሳቱን መግለጽ እንዳለበት እናምናለን።ማቴዎስ 28:18-20

14ዳግም የተወለደ አማኝ ሁሉ የጌታ እራትን በመካፈል ጌታ ዳግም እስኪመጣ ሞቱንና ትንሳኤውን እንዲሁም ከአማኞች ጋር ያለውን ኅብረት መግለጽ እንዳለበት እናምናለን፡፡ማቴዎስ 26: 26-28

15-  ቅዱሳን መላእክት የእግዚአብሔርን ሕዝብ እንደሚጠብቁና እንደሚረዱ እናምናለን። መዝሙር 34:7፣ 91:11፣ ማቴዎስ 18:10፣ እብራውያን 1:14

16- ሰይጣንና ሌሎች የወደቁ መላእክት ክፉዎችና አደገኞች እንደሆኑ፤ ነገር ግን ክርስቶስ እንዳሸነፋቸውና እንደተፈረደባቸው እናምናለን። ኤፌሶን 6: 10-18፤ ቆላስይስ 2: 15፤ 1 ጴጥሮስ 5: 8፤ ራእይ 12: 10-12

17ክርስቶስ በግልጽ እንደሚመለስና ሙታን እንደሚነሱ እናምናለን። ማቴዎስ 24:30፣ 1 ቈረ. 15:52፣ 1 ተሰሎንቄ 4:16 ራእይ 21:1-5

18- ቅዱሳን በአዲሱ ሰማይና በአዲሱ ምድር ደስ እያላቸው ለዘላለም እንደሚኖሩ፤ ኃጥአን ግን በገሃነም ውስጥ ለዘላለም እንደሚሰቃዩ እናምናለን፡፡ ዳንኤል 12:2-3 ማቴዎስ 25:31-46 ራእይ 22:1-5 2 ተሰሎንቄ 1:9


19-  ክርስቲያናዊ ጋብቻ የአንድ ወንድና የአንዲት ሴት የዕድሜ ልክ ጥምረት እንደሆነና ከጋብቻ ውጭ የሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የተከለከለ እና ኃጢአት መሆኑን እናምናለን። ዘፍጥረት 2:22-25፣ ማቴዎስ 5:27-32፣ ማቴዎስ 19:3-9 1 ቈረንቶስ 7:1-11


20 እግዚአብሔርን በመፍራትና በቅድስና ሕይወት እንድንመላለስ እግዚአብሔር እንደ ጠራን እናምናለን። መዝሙር 24:1 ቈሎሴ 3:17 2 ቈረንቶስ 10:5


21 እግዚአብሔር ለህዝብ ሁሉ ወንጌልን እንድናደርስ እና እያስተማርን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንድናደርግ እንደጠራን እናምናለን። መዝሙር 96:3፣ ማቴዎስ 5:14፣ ማቴዎስ 28:18-20፣ 1 ጴጥሮስ 3:15