- Get link
- X
- Other Apps
የእምነት አቋም
1- መጽሐፍ ቅዱስ (66 መጽሐፍት) ትክክለኛ እና እውነተኛ እንዲሁም የማይለወጥ የእግዚአብሔር አስትንፋሳዊ ቃል እንደሆነ እናምናለን፡፡ ስለሆነም ብቸኛ የእምነት እና የሕይወት የመጨረሻ ሥልጣን አለው። ምሳሌ 30:5-6፤ ኢሳይያስ 8:20፤ ዮሐንስ 10:35፤ 2 ጢሞቴዎስ 3:16-17፤ 2 ጴጥሮስ 1:21
2- እግዚአብሔር በአንድነትና በሶስትነት ለዘላለም ጸንቶ የሚኖር አምላክ እንደሆነ፤ በመለኮት አንድ ሲሆን በአካል ሶስት እንደሆነ እናምናለን (አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ)፡፡ ዘዳግም 6:4፣ ማቴዎስ 28:19፣ ዮሃንስ 14:26፣ 2 ቈረንቶስ 13:14፡፡
3- እግዚአብሔር አብ አባት ሲሆን ሁሉን የሚችልና ሁሉን የሚገዛ ዘላለማዊ አምላክ እንደ ሆነ እናምናለን፡፡
4- እግዚአብሔር አጽናፈ አለምን ከምንም እንደፈጠረና ፍጥረትም ሁሉ ከመጀመሪያ መልካም እንደ ነበረ እናምናለን። ዘፍጥረት 1-2፣ ዘጸአት 20:11፣ እብራውያን 11:3
5- እግዚአብሄር ሰውን በአምሳሉና በመልኩ እንደ ፈጠረ እንዲሁም የፍጥረት ሁሉ ገዥ እንዳደረገው እናምናለን። ዘፍጥረት 1:26-28፣ መዝሙር 8፣ ኢሳይያስ 43:7፣ ራእይ 4:11፣ መዝሙር 37:4
6- ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተስፋው ቃል የእስራኤል መሲሕ እንደሆነና ፍፁም አምላክ፣ ፍፁም ሰው እንደሆነ እናምናለን። ማቴዎስ 1:21-23፣ ዮሃንስ 1:1, 14፣ 20: 28፣ እብራውያን 1:1-4፣ 2:14
7- ኢየሱስ ከድንግል እንደተወለደና ለአብ ፈጽሞ እንደታዘዘ እናምናለን፤ እንዲሁም ድንቅና ተአምራትን እንዳደረገ፣ በመስቀል ላይ እንደ ሞተ፣ በሶስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ እንደ ተነሳና ወደ ሰማይ አርጎ በሁሉ ላይ እንደ ነገሰ እናምናለን። ሉቃስ 1:26-35፣ እብራውያን 4:15፣ ዮሃንስ 14:11፣ ሉቃስ 23-24፣ ኤፌሶን 1:20-23
8- መንፈስ ቅዱስ ልክ እንደ አብ እና ወልድ የመለኮት ባሕርያት ሁሉ ያሉት ፍጹም አምላክ እንደሆነና አምልኮ እንዲሁም ስግደት እንድሚገባው እናምናለን፡፡
9- ሰው በኃጢአት እንደ ወደቀና እራሱን ማዳን እንደማይችል እናምናለን። ዘፍጥረት 3፣ ሮሜ 3:12, 23፣ ሮሜ 5:12
10- መዳን ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ስጦታ ስለሆነ በክርስቶስ በማመን ምንቀበለው እንጅ በስራ እንደማናገኘው እናምናለን። ዮሃንስ 3:16፣ ሮሜ 1:16-17፣ ገላትያ 2:16-21
11- መንፈስ ቅዱስ አዲስ ልደት እንደሰጠንና ከክርስቶስ ጋር አንድ አካል እንዳደረገን፣ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ፍቅር እንደሚያረጋግጥልን፣ ወደ እውነት እንደሚመራን፣ በጸጋ ስጦታዎቹ እንደሚያስታጥቀንና ኃይል እንደሚሰጠን እናምናለንል። ዮሃንስ 3:3-8፣ ግብሪ ሃዋርያት 1:8፣ ሮሜ 8፣ 1 ቈረንቶስ 12፣ ገላትያ 5:16-26፣ ኤፌሶን 3:16-21
12- ቤተ ክርስቲያን በዘመናት መካከል ከሕዛብ ሁሉ በክርስቶስ የተጠሩ ሰዎች ህብረትና የክርስቶስ አካል እንደሆነች እናምናልን። ሮሜ 12:5፣ ገላትያ 3:26-29፣ ኤፌሶን 1:22-23፣ ራእይ 7:9
13- ዳግም የተወለደ አማኝ ሁሉ በአብ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም በውኃ በመጠመቅ ከክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ጋር መተባበሩን እንዲሁም ለኃጢአት ሞቶ ለጽድቅ መነሳቱን መግለጽ እንዳለበት እናምናለን።ማቴዎስ 28:18-20
14- ዳግም የተወለደ አማኝ ሁሉ የጌታ እራትን በመካፈል ጌታ ዳግም እስኪመጣ ሞቱንና ትንሳኤውን እንዲሁም ከአማኞች ጋር ያለውን ኅብረት መግለጽ እንዳለበት እናምናለን፡፡ማቴዎስ 26: 26-28
15- ቅዱሳን መላእክት የእግዚአብሔርን ሕዝብ እንደሚጠብቁና እንደሚረዱ እናምናለን። መዝሙር 34:7፣ 91:11፣ ማቴዎስ 18:10፣ እብራውያን 1:14
16- ሰይጣንና ሌሎች የወደቁ መላእክት ክፉዎችና አደገኞች እንደሆኑ፤ ነገር ግን ክርስቶስ እንዳሸነፋቸውና እንደተፈረደባቸው እናምናለን። ኤፌሶን 6: 10-18፤ ቆላስይስ 2: 15፤ 1 ጴጥሮስ 5: 8፤ ራእይ 12: 10-12
17- ክርስቶስ በግልጽ እንደሚመለስና ሙታን እንደሚነሱ እናምናለን። ማቴዎስ 24:30፣ 1 ቈረ. 15:52፣ 1 ተሰሎንቄ 4:16፣ ራእይ 21:1-5
18- ቅዱሳን በአዲሱ ሰማይና በአዲሱ ምድር ደስ እያላቸው ለዘላለም እንደሚኖሩ፤ ኃጥአን ግን በገሃነም ውስጥ ለዘላለም እንደሚሰቃዩ እናምናለን፡፡ ዳንኤል 12:2-3፤ ማቴዎስ 25:31-46፤ ራእይ 22:1-5፤ 2 ተሰሎንቄ 1:9
19- ክርስቲያናዊ ጋብቻ የአንድ ወንድና የአንዲት
ሴት የዕድሜ ልክ ጥምረት እንደሆነና ከጋብቻ ውጭ የሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የተከለከለ እና ኃጢአት መሆኑን እናምናለን። ዘፍጥረት
2:22-25፣ ማቴዎስ 5:27-32፣ ማቴዎስ 19:3-9፣ 1 ቈረንቶስ 7:1-11
20- እግዚአብሔርን በመፍራትና በቅድስና
ሕይወት እንድንመላለስ እግዚአብሔር እንደ ጠራን እናምናለን። መዝሙር 24:1፣ ቈሎሴ 3:17፣ 2 ቈረንቶስ 10:5
21- እግዚአብሔር ለህዝብ ሁሉ ወንጌልን
እንድናደርስ እና እያስተማርን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንድናደርግ እንደጠራን እናምናለን። መዝሙር 96:3፣ ማቴዎስ 5:14፣
ማቴዎስ 28:18-20፣ 1 ጴጥሮስ 3:15
- Get link
- X
- Other Apps
Comments
Post a Comment